🚩መቀመጫውን በሀገረ አሜሪካ ማሳቹሴትስ ያደረገው ኢቮልቭ የተባለ የቴክኖሎጂ ተቋም ትምህርት ቤቶች፣ ስቴዲየሞች እና ሰዎች በብዛት የሚገኙባቸውን መሰል ሥፍራዎች ደህንነት ለማስጠበቅ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ጥቅም ላይ አውሏል፡፡
🚩በእነዚህ ሥፍራዎች ለመገልገል የሚመጡ ሰዎች በተለመደው የፍተሻ አይነት ማለፍ አይጠበቅባቸውም፡፡ ይልቁንም በግራ እና ቀኝ በቆሙ ሁለት ሰሌዳዎች መካከል ያለምንም ንክኪ፣ ሰልፍ እና እንግልት በማለፍ ይስተናገዳሉ፡፡
🚩ቴክኖሎጂው የሚሰራው እጅግ የተራቀቁ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መጠቆሚያዎችን (ሴንሰር) ከካሜራዎች ጋር በማቀናጀት እንደሆነ ፎክስ ኒውስ ዘግቧል፡፡
🚩በዚህም ምንም አይነት ጉዳት የሌላቸውን ብረት ነክ ቁሳቁሶች ከሽጉጥ፣ ከስለት እና ተቀጣጣይ መሣሪያዎች በመለየት ለሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ የማንቂያ መልዕክት ይልካል፡፡
🚩ይህም በብዙ ሥፍራዎች የሚገኙትን የብረት ነክ ቁሳቁሶችን በአጠቃላይ እንደ አደገኛ መሣሪያ በመቁጠር የፍተሻ አገልግሎት ከሚሰጡ መሣሪያዎች በእጅጉ እንዲለይ አስችሎታል፡፡
🚩ተቋሙ ከአውሮፓውያኑ 2019 ጀምሮ በስፖርት ውድድር መታደሚያ ሥፍራዎች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሰል ስፍራዎች ቴክኖሎጂውን ተግባራዊ በማድረግ ሦስት መቶ ሚሊዮን ሰዎች መፈተሸ መቻሉን አስታውቋል፡፡ @SSWSIT



No comments:
Post a Comment